Apr 26, 2016

ፎረም 65፦ ዶሮና አለመግባባት በዲያስፓራ (እንግዳ ተሳታፊ፦ አቶ ግርማ ጉተማ) ክፍል 1

የዶሮ እርባታ አክሲዮን የፈጠረው ውዝግብ ለዱያስፓራ ፓለቲካዊ አለመግባባት ሌላ ማስረጃ ሆኖ ሰነባብቷል። አለመግባባት በዲያስፓራ አዲስ ክስተት አይደለም። ኢትዮጵያውያን አገር ውስጥ ያጣነውን የሃሳብ መግለፅ ነፃነት በውጪ አገራት ስናገኝ ወደ መግባባት ሳይሆን ወደ አለመግባባት ፤ ወደ ትብብር ሳይሆን ወደ ክፍፍል ፤ ወደ ውጤታማነት ሳይሆን ወደ እንቅፋትነት የምናዘነብል ይመስላል ። ይህ ለምን ይሆናል?

በዛሬው የፎረም 65 ውይይት "አለመግባባት በዲያስፓራ" በሚል ርዕስ ውይይት እናደርጋለን። እንግዳ ተሳታፊያችን አቶ ግርማ ጉተማ ነው። አቶ ግርማ በፌስቡክና በት ዊተር በፓለቲካ ውይይቶች ላይ ሰፊ ተሳትፎ ከሚያደርጉ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አንዱ ነው።






ተልዕኳችን | Our Mission

“65 ፐርሰንት” ትርጉም? የኢትዮጵያ ህዝብ 65 በመቶው እድሜያቸው ከ24 አመት በታች ነው። ተልዕኳችን ለመጪው ትውልድ የመግባባትን ፓለቲካ በአርአያነት ማውረስ ነው። ግባችን ለፓለቲካዊ እርቅና መግባባት መሟገትና ፋና ወጊ መሆን ነው።

What is “65 percent”? 65% of Ethiopia’s population is under 24 years old. Our mission is to model a culture of political concensus for the 65%. Our goal is to advocate for, and initiate reconciliation and consensus among Ethiopians.

Post Archive