Jun 28, 2018

ፎረም 65፦ ሰብዓዊ መብቶች ለምን አልተከበሩም? #Ethiopia #Forum65

በህገ-መንግስት ውስጥ የተጎናጸፉ ሰብዓዊ መብቶችስ ለምን አልተከበሩም፣ እንዴትስ መከበር ይችላሉ? በዚህ ጉዳይ ላይ ሙያዊ ሃሳቡን እንዲያጋራን እንግዳችን የሰብዓዊ መብት የህግ ባለሙያ ዶ/ር አባድር ኢብራሂም ነው። ዶ/ር አባድር የCenter for the Advancement of Human rights and Democracy in Ethiopia ዳይሬክተር እና የኢትዮጵያ የዕርቅና የርትዓዊ ፍትህ ምክርር ቤት አባል ነው።


Jun 27, 2018

ፎረም 65፦ የሰላምና ዕርቅ ጥሪ ከእምነት አባቶች #Ethiopia #Forum65

እንግዶቻችን ሼክ ካሊድ መሀመድ ኦመር የFirst Hijra Foundation ኢማም ፡ ከዋሽንግተን ዲሲ እና አባ ገብረኪዳን ከሚኒሶታ ደብረብርሃን ቅዱስ ኡራኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ሴንት ፓል ሚኒሶታ ናቸው። 


Jun 26, 2018

Jun 25, 2018

ፎረም 65፦ የሰኔ 16 ድጋፍ ሰልፍና እንድምታው #Ethiopia #Forum65

ቅዳሜ ሰኔ 16 አዲስ አበባ ከተደርገው ሰልፍ ጋር በተያያዘ በማህበራዊ ሚዲያ ሰፊ ተሳትፎ ከሚያደርጉት ከአቶ አሉላ ሰሎምን ከዩናይትድ ስቴትስ እና አቶ ዳንኤል ብርሃነ የ HornAffairs.com ዋና አዘጋጅ ከአዲስ አበባ በፎረም 65 ላይ ቀርበው ሰልፉን አስመልክቶ የተሰማቸውን ስሜትና እንዲሁም ማስተላለፍ የሚፈልጉት መልዕክት ካለ እድል መስጠቱ ከሀገራዊ መግባባትና ወንድማማችነት አንጻር ጠቃሚ ሆኖ ስላገኘነው ጋብዘናቸዋል።


Jun 24, 2018

Jun 20, 2018

ፎረም 65፦ እስርና መዘዙ (ልዩ ዝግጅት)

መታሰር መዘዙ ምንድን ነው? ስነልቦናዊ ፣ አካላዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ ፣ ቤተሰባዊና ማህበራዊ የኑሮ ላይ ምን አይነት መዘዝ ያስከትላል? የቀድሞ ታሳሪዎች ምን አይነት ፍትህ ይሻሉ? እንግዶቻችን ወ/ት ጫልቱ ታከለ ፣ አቶ ዮናታን ተስፋየና አቶ ነሲቡ ስብሃት ናቸው።



Jun 13, 2018

Jun 8, 2018

ፎረም 65፦ ዓብይ የዲያስፓራውን ፓለቲካ ያቃሉን? #Ethiopia #Forum65

አገር ውስጥ ያለውን የፓለቲካ ሂደትና የዲያስፓራውን ሚና በሚመለከት ከኢሕአዴግ ደጋፊዎች እንግዶቻችን ጋር ውይይት አዘጋጅተናል። እንግዶቻችን አቶ አሉላ ሰለሞንና አቶ እስራዔል ገደቡ ናቸው።


Jun 7, 2018

ፎረም 65፦ የዲያስፓራ ሚና በዘመነ ዓብይ #Ethiopia #Forum65

አገር ውስጥ ያለውን የፓለቲካ ሂደትና የዲያስፓራውን ሚና በሚመለከት ከተንፎካካሪው ጎራ እንግዶቻችን ጋር ውይይት አዘጋጅተናል። እንግዶቻችን አቶ ገረሱ ቱፋ ከኔዘርላንድ፣ ዶ/ር ኢዮብ ገብረመስቀል ከብሪታኒያ እና አቶ ግርማ ካሳ ከዩናይትድ ስቴትስ ናቸው።


ተልዕኳችን | Our Mission

“65 ፐርሰንት” ትርጉም? የኢትዮጵያ ህዝብ 65 በመቶው እድሜያቸው ከ24 አመት በታች ነው። ተልዕኳችን ለመጪው ትውልድ የመግባባትን ፓለቲካ በአርአያነት ማውረስ ነው። ግባችን ለፓለቲካዊ እርቅና መግባባት መሟገትና ፋና ወጊ መሆን ነው።

What is “65 percent”? 65% of Ethiopia’s population is under 24 years old. Our mission is to model a culture of political concensus for the 65%. Our goal is to advocate for, and initiate reconciliation and consensus among Ethiopians.

Post Archive