Feb 26, 2018

Ethiopia ፎረም 65፦ ከቀጣዩ ጠ/ሚ ምን ይጠበቃል? #Forum65 #Ethiopia

ሀገራዊ ፓለቲካዊ ቀውስ በኢትዮጵያ በተስፋፋበትና ዳግም አስቸኳይ አዋጅ በታወጀበት በአሁኑ ወቅት ፡ ከቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ምን ይጠበቃል? ውይይቱን ያድምጡ! ከኢትዮጵያ በአነስተኛ ሜጋባይት ውይይቱን እዚህ https://goo.gl/CNgBAq ያድምጡ። (መጠን፦ 3.62 MB) Telegram: https://t.me/forum65


Feb 19, 2018

ፎረም 65፦ ኢትዮጵያ ወዴት? እንዴት? (እንግዳ አቶ ልደቱ አያሌው)

ሀገራችን መሰረታዊ የለውጥ እድልና አጋጣሚ ወቅት ላይ ትገኛለች። የለውጥ አቅጣጫው ወዴት ነው? ወደ ለውጥ ግቡ እንዴት እንድረስ? ከአቶ ልደቱ አያሌው ጋር የሚከተሉትን ነጥቦች ዳስሰናል፦ 1. የአቶ ለማና ኦሕዴድ ፓለቲካ እንድምታው 2. የሀገራዊ መግባባት ኮሚሽን መመስረት አስፈላጊነት 3. በተቃዋሚው ውስጣዊ መግባባት እንዲፈጠር 4. የኢሕአዴግ መሪዎችና አባላት ዋስትና ጉዳይ።


[ከኢትዮጵያ በአነስተኛ ሜጋባይት ውይይቱን እዚህ https://goo.gl/SjC1ws ያድምጡ። (መጠን፦ 7.99 MB)]

[✆ አስተያየት አለዎት? ይደውሉልን፦ +001-929-367-8665 ☎ Viber, WhatsApp, Telegram ላይ አለን። ☏ በቀጥታም በስልክ መልዕክት ይላኩልን።]


Feb 9, 2018

ፎረም 65፦ የዐማራ-ኦሮሞ አጋርነት በነገዋ ኢትዮጵያ

በተቃዋሚው ጎራ የሚገኙ ዐማራና ኦሮሞ ሊሂቃን ከጊዜያዊና ስልታዊ አጋርነት ወደ ዘላቂና ስትራቴጂክ አጋርነት ለመሸጋግር የኦሮሞ ሊሂቃን ከዐማራ ሊሂቃን ምን ይጠብቃሉ? የአለመግባባት ምክንያቶች ምንድን ናቸው?  ከትናንቷ ፡ ከዛሬዋና ከመጪዋ ኢትዮጵያ አንጻር የአለመግባባት መንስኤዎችን ለመዳሰስና የመፍትሄ ሃሳባቸውን እንዲጠቁሙ ሁለት ኦሮሞ ወገኖች በፎረም 65 ጋብዘናል። እንግዶቻችን ዶ/ር በያን አሶባ ከዩናይትድ ስቴትስ እና አክቲቪስት አቶ ገረሱ ቱፋ ከኔዘርላንድ ናቸው። ውይይቱን ያድምጡ!
[ከኢትዮጵያ በአነስተኛ ሜጋባይት ውይይቱን እዚህ https://goo.gl/CsqaZJ ያድምጡ። (መጠን፦ 10.2 MB)]
[✆ አስተያየት አለዎት? ይደውሉልን፦ +001-929-367-8665 ☎ Viber, WhatsApp, Telegram ላይ አለን። ☏ በቀጥታም በስልክ መልዕክት ይላኩልን።]


ተልዕኳችን | Our Mission

“65 ፐርሰንት” ትርጉም? የኢትዮጵያ ህዝብ 65 በመቶው እድሜያቸው ከ24 አመት በታች ነው። ተልዕኳችን ለመጪው ትውልድ የመግባባትን ፓለቲካ በአርአያነት ማውረስ ነው። ግባችን ለፓለቲካዊ እርቅና መግባባት መሟገትና ፋና ወጊ መሆን ነው።

What is “65 percent”? 65% of Ethiopia’s population is under 24 years old. Our mission is to model a culture of political concensus for the 65%. Our goal is to advocate for, and initiate reconciliation and consensus among Ethiopians.

Post Archive