የኦሮሞ ተቃውሞ አንደኛ አመት መታሰቢያ በማድረግ ከሁለት ኦሮሞ አክቲቪስትቶ ጋር ውይይት አድርገናል። እንግዶቻችን አቶ ገረሱ ቱፋ እና አቶ ግዛቸው ኢብሳ ናቸው።
Oct 28, 2016
Oct 24, 2016
ፎረም 65፦ ኢትዮጵያዊነት
Posted on October 24, 2016
ባለፉት 25 ዓመታት ኢሕአዴግ በብሄር ማንነቶች ላይ ትኩረት በማድረግ ኢትዮጵያዊነትን ችላ ብሏል የሚል ትችት በሰፊ ይሰማል። ፎረም 65 ኢትዮጵያዊነት ላይ ከሚያተኩሩ ስብስቦች ውስጥ ሁለት እንግዶች ጋብዘናል።
እንግዶቻችን ዶ/ር እርቁ ይመር "ኢትዮጵያዊነት የዜጎች መብት ማስከበሪያ ጉባኤ" ሊቀመንበር ፤ ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ የ"አንድ ኢትዮጵያ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ" አስተባባሪ ናቸው።
እንግዶቻችን ዶ/ር እርቁ ይመር "ኢትዮጵያዊነት የዜጎች መብት ማስከበሪያ ጉባኤ" ሊቀመንበር ፤ ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ የ"አንድ ኢትዮጵያ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ" አስተባባሪ ናቸው።
Oct 15, 2016
ፎረም 65፦ ህወሓት፣ ትግራይና ዲያስፓራ
Posted on October 15, 2016
በዲያሥፓራ የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጆች የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሕዝባዊ ተቃውሞዎችን አስመልክቶ በተከታታይ ያወጧቸውን መግላጫዎችን በሚመለከት ከአቶ በየነ ገብራይ እና አቶ የማነ ምትኩ ጋር ቆይታ አድርገናል።
[ማስተካከያ፦ አቶ በየነ ገብራይ የኢሮብ ብሄር ናቸው። በቅጂው ላይ አቶ በየነን ትግራዋይ የሚለው ኢሮብ በሚለው ይስተካከል። ከይቅርታ ጋር!]
[ማስተካከያ፦ አቶ በየነ ገብራይ የኢሮብ ብሄር ናቸው። በቅጂው ላይ አቶ በየነን ትግራዋይ የሚለው ኢሮብ በሚለው ይስተካከል። ከይቅርታ ጋር!]
Oct 7, 2016
ፎረም 65፦ ሰላማዊ ትግል - ትርፍ ወይስ ኪሳራ?
Posted on October 07, 2016
የኢሬቻ በዓል ወቅት የብዙዎችን መሞትና መቁስል አስከትሎ የሰላማዊ ትግል አያዋጣንም የሚሉ እይታዎች እየተገለጹ ነው። "ሰላማዊ ትግል፦ ትርፍ ወይስ ኪሳራ?" በሚል ከአቶ አሰፋ ጫቦ፡ አቶ ፈቃደ ሸዋቀና እና አቶ ዳዊት ተሾመ ጋር ውይይት አድርገናል።
Oct 4, 2016
ፎረም 65፦ ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት - አቶ ተክሌ ይሻው
Posted on October 04, 2016
በፎረም 65 ከአቶ ተክሌ ይሻው ጋር በዐማራ ሕዝብ ጥቅም፣ በዐማራ-ኦሮሞ አጋርነትና በዐማራነትና ኢትዮጵያዊነት ላይ አጭር ቆይታ አድርገናል። አቶ ተክሌ ይሻው የሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ሊቀመንበር ናቸው።
ስለድርጅቱ መረጃ ለማግኘት ድረገጹን ይጎብኙ፦ http://www.moreshwegenie.org/
ስለድርጅቱ መረጃ ለማግኘት ድረገጹን ይጎብኙ፦ http://www.moreshwegenie.org/
Subscribe to:
Posts (Atom)
ተልዕኳችን | Our Mission
“65 ፐርሰንት” ትርጉም? የኢትዮጵያ ህዝብ 65 በመቶው እድሜያቸው ከ24 አመት በታች ነው። ተልዕኳችን ለመጪው ትውልድ የመግባባትን ፓለቲካ በአርአያነት ማውረስ ነው። ግባችን ለፓለቲካዊ እርቅና መግባባት መሟገትና ፋና ወጊ መሆን ነው።
What is “65 percent”? 65% of Ethiopia’s population is under 24 years old. Our mission is to model a culture of political concensus for the 65%. Our goal is to advocate for, and initiate reconciliation and consensus among Ethiopians.