ባለፉት ጥቂት ተከታታይ ጽሁፎች ላይ እንደተወያየነው በስምምነት ላይ የተመሰረተ ባህላዊ ውህደት ውስጥ መግባት ኢትዮጵያን እንደገና ለማነጽ ኣማራጭ መፍትሄ ይሆናል። ታዲያ በስምምነት ላይ የተመሰረተ ባህላዊ ውህደት ላሉብን ውስብስብ ሁለንተናዊችግሮች ሁሉ መፍትሄ ይሆናል ማለት ሳይሆን ቅድሚያ ተሰጥቷቸው ሊፈቱ የሚገባቸውን ባህላዊ ማህበራዊ ችግሮች መስመር በማስያዝ በሂደት እየተፈቱ እንዲሄዱ ከማድረጉም በላይ ሌሎች ችግሮችን ለመፍታት ደግሞ ቀጥተኛ ያልሆነ ኣስተዋጾ ስላለው
ነው። በችግር ኣፈታት ጊዜ ከሚመጡት መፍትሄዎች መካከል የትኛውን ብናስቀድም ነው ሌላውን ችግርም ኣብሮ ሊፈታልን የሚችለው ብለንም እንጠይቃለንና በዚህ ረገድ በስምምነት ላይ የተመሰረተ ባህላዊ ውህደት ውስጥ መግባት ሌሎች መጋቢና
ተለጣጣቂ ችግሮችን ለመፍታት ይጠቅማል ከሚል ነው። ተጨማሪ ያንብቡ
ምንጭ፦ http://www.ethiomedia.com/14store/bherawi_erq.pdf
