May 25, 2016

ፎረም 65፦ የፓልቶክ ሚናና አገራዊ መግባባት (እንግዶች፦ ሎሬትና ኢዛና)

"የፓልቶክ ሚናና አገራዊ መግባባት" በሚል ርዕስ ውይይት እናደርጋለን። እንግዳ ተሳታፊዎቻችን አቶ ሸመልስ በዛብህ (የፓልቶክ መጠሪያ "ሎሬትፀጋዬ") እና አቶ እስራኤል ገደቡ (የፓልቶክ መጠሪያ "ኢዛና") ናቸው።








May 24, 2016

ፎረም 65፦ የሁለት ትግራዋይ እይታዎች - ክፍል 2

በፎረም65 ሁለት ሳምንታት በፊት ሜይ 3፣ 2016 እ.አ.አ "በዲያስፓራ የትግራይ ጥላቻ አለን?" በሚል ርዕስ ተወያይተን ነበር። ውይይቱ በድረገፃችን www.65Percent.org ላይ ይገኛል። የውይይቱ ጉዳይ ላይ የትግራዋይ እይታም መደመጥ አለበት ብለን ስለምናምን ዛሬ ሁለት ትግራዋይ ወገኖቻችንን በፎረም65 ለውይይት ጋብዘናል። እንግዶቻችን አቶ ግደይ ዘራፅዮን ከኖርዌይ እና አቶ አብርሃም አሰፋ ከኢትዮጵያ ናቸው።










May 20, 2016

ፎረም 65፦ የሁለት ትግራዋይ እይታዎች - ክፍል 1

በፎረም65 ሁለት ሳምንታት በፊት ሜይ 3፣ 2016 እ.አ.አ "በዲያስፓራ የትግራይ ጥላቻ አለን?" በሚል ርዕስ ተወያይተን ነበር። ውይይቱ በድረገፃችን www.65Percent.org ላይ ይገኛል። የውይይቱ ጉዳይ ላይ የትግራዋይ እይታም መደመጥ አለበት ብለን ስለምናምን ዛሬ ሁለት ትግራዋይ ወገኖቻችንን በፎረም65 ለውይይት ጋብዘናል። እንግዶቻችን አቶ ግደይ ዘራፅዮን ከኖርዌይ እና አቶ አብርሃም አሰፋ ከኢትዮጵያ ናቸው።








May 16, 2016

May 11, 2016

ፎረም 65፦ የአቶ በቀለ ገርባ ክስ (እንግዳ ተሳታፊ፦ አቶ እሸቱ ሆማ) ክፍል 1

መንግስት በአቶ በቀለ ገርባ ላይ የመሰረታቸው ክሶችን ምንድን ናቸው? አቶ በቀለ ገርባ ከዚህ በፊት 4 ዓመታት ታስረው ነበር። ያሁኑን ክስ ልዩ ሚያደርገው ነገር አለ?

ክስ የተመሰረተባቸው አቶ በቀለ ገርባና አቶ ዮናታን ተስፋዬ ረጋሳና ሌሎች ዜጎች ጉዳይ ባጠቃላይ ስለመንግስት ባህሪ ምን ያመለክታል? ተከሳሽሾች ከኦሮሞነታቸው የተነሳ ብቻ ነው የታሰሩት ሚለው ትችት መሰረት አለውን? በተለይ አቶ ዮናታንን ከኦነግ ጋር የሚያገናኝ ክስ ተመስርቷል። አቶ ዮናታን ግን የሰማያዊ ፓርቲ አባል ነው። ይሄንን እንዴት ታዩታላችሁ?

የዛሬው የፎረም65 ውይይት እንግዳ ተሳታፊያችን አቶ እሸቱ ሆማ አገራዊ ጉዳዮች ላይ በፌስቡክ በሰፊው ከሚሳተፉ ወገኖች አንዱ ነው። አቶ እሸቱ የህግ ባለሙያ ነው።






May 3, 2016

ፎረም 65፦ አለመግባባት በዲያስፓራ (እንግዳ ተሳታፊ፦ አቶ ግርማ ጉተማ) - ክፍል 2

በዲያስፓራ ትግራይ ላይ ያነጣጠረ ጥላቻ አለን? ተቃዋሚዎች የትግራይ ሕዝብ የከፈለውን መስዋዕትነት ያረክሳሉን? የትግራዋይ ድምጽ በብዛት በተቃዋሚነት ማይሰማው ህወሃት ከሚያደርስባቸው ቁጥጥርና እንዲሁም ከድህነት የተነሳ ነውን?








Apr 26, 2016

ፎረም 65፦ ዶሮና አለመግባባት በዲያስፓራ (እንግዳ ተሳታፊ፦ አቶ ግርማ ጉተማ) ክፍል 1

የዶሮ እርባታ አክሲዮን የፈጠረው ውዝግብ ለዱያስፓራ ፓለቲካዊ አለመግባባት ሌላ ማስረጃ ሆኖ ሰነባብቷል። አለመግባባት በዲያስፓራ አዲስ ክስተት አይደለም። ኢትዮጵያውያን አገር ውስጥ ያጣነውን የሃሳብ መግለፅ ነፃነት በውጪ አገራት ስናገኝ ወደ መግባባት ሳይሆን ወደ አለመግባባት ፤ ወደ ትብብር ሳይሆን ወደ ክፍፍል ፤ ወደ ውጤታማነት ሳይሆን ወደ እንቅፋትነት የምናዘነብል ይመስላል ። ይህ ለምን ይሆናል?

በዛሬው የፎረም 65 ውይይት "አለመግባባት በዲያስፓራ" በሚል ርዕስ ውይይት እናደርጋለን። እንግዳ ተሳታፊያችን አቶ ግርማ ጉተማ ነው። አቶ ግርማ በፌስቡክና በት ዊተር በፓለቲካ ውይይቶች ላይ ሰፊ ተሳትፎ ከሚያደርጉ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አንዱ ነው።






Apr 20, 2016

Apr 19, 2016

ፎረም 65፦ ስለጋምቤላ የሀዘን መግለጫ


በጋምቤላ ክልል በወገኖቻችን ላይ በደረሰው አሰቃቃቂ የጅምላ ግድያ የተሰማንን ጥልቅ ሃዘናችንን እንገልጻለን።

አድማጮቻችን በጋምቤላ በደረሰው የጅምላ ግድያ ላይ የተሰማችሁን ስሜት በስልክ ቁጥራችን 929-367-8665 ደውላችሁ እንድትገልጹ በትህትና እንጋብዛለን።



Apr 18, 2016

ተልዕኳችን | Our Mission

“65 ፐርሰንት” ትርጉም? የኢትዮጵያ ህዝብ 65 በመቶው እድሜያቸው ከ24 አመት በታች ነው። ተልዕኳችን ለመጪው ትውልድ የመግባባትን ፓለቲካ በአርአያነት ማውረስ ነው። ግባችን ለፓለቲካዊ እርቅና መግባባት መሟገትና ፋና ወጊ መሆን ነው።

What is “65 percent”? 65% of Ethiopia’s population is under 24 years old. Our mission is to model a culture of political concensus for the 65%. Our goal is to advocate for, and initiate reconciliation and consensus among Ethiopians.

Post Archive